ቅድስት ሰማእት አርሴማ
የቅድስት ሰማእት አርሴማ blogspot
Thursday, December 1, 2011
Saturday, September 3, 2011
Wednesday, July 6, 2011
የቅድስት አርሴማ ታሪክ በአጭሩ
እናታችን ቅድስት አርሴማ እግዚአብሔርን በቅንነት ያገለግሉ ከነበሩ ከከበሩ ካህናት ወገን ከሆኑ ከቅዱስ ቴዎድሮስና ከእናቷ ቅድስት አትናሲያ በስዕለት ተወለደች፡፡
ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ብሉይን ሐዲስን ተምራ እያነበበች እንዲሁም በተግባር እየተረጎመች ዘወትርም በጸሎት ትተጋ እንደነበር ገድሏ ይተርካል፡፡ በዚህ ዘመን ድርጣድስ የሚባል በአርመን የነገሠ አረማዊ ንጉሥ ለጣዖት የሚሰግድ' ፀሐይንም የሚያመልክ' ክርስቲያኖችንም እኔ ለማመልከው አምላክ መስገድ አለባችሁ በማለት መከራ ያጸናባቸው ነበር፡፡
እናታችን ቅድስት አርሴማም ተጋድሎዋን የጀመረችው የዚህ ጨካኝ ንጉሥ አገልጋይ ወይም ሹም ፳፯ ክርስቲያኖችን እንደልማዱ እየደበደበ' እየገረፈና ልዩ ልዩ ስቃይ እያደረሰባቸው ሲወስዳቸው በማየቷ ነበር፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‘‘ለእነርሱና ለአሕዛብ ምስክር እንዲሆን ስለኔ ወደገዢዎችና ወደ ነገሥታት ትወሰዳላችሁ፡፡’’ (ማቴ. ፲፡፲፮፡፲፱)፡፡ ያለውን በማሰብ ቅድስት አርሴማም ገና በሃያ ዓመቷ የዚህን ዓለም ንጉሥ እኩይ ግብሩን በመንቀፍ ስለ ክርስቶስ ከሚሰቃዩ ወገኖቿ ጋር ግንባር ቀደም በመሆን ትመሰክር ጀመር፡፡ የንጉሡም አገልጋይ በደም ግባቷና በንግግሯ ማማር ተደንቆ በዚች በፈቃዷ ልትሠዋ በወደደች ሴት ምንም ሊያደርግባት ስላልወደደ ወደ ንጉሡ ወደ ድርጣድስ ከሃያ ሰባቱ ክርስቲያኖች ጋር ወሰዳት፡፡ ንጉሡም ብዙ የተነገረላትን ወጣት ሲያይ በውበቷና በንግግሯ ተማርኮ ለዓለማዊ ደስታውና ፍላጎቱ ተመኛት፡፡ ለእርሱም ሙሽራ እንድትሆን ብዙ ወተወታት፡፡ ቅድስት አርሴማ ግን ናቀችው ‘‘እኔ የሰማያዊው ንጉሥ የክርስቶስ ሙሽራ እንጂ የዚህን ዓለም አላፊ ጠፊ የሆነውን ገንዘብና ደስታ የምሻ አይደለሁም፡፡’’ በማለትም መለሰችለት፡፡
ንጉሡም ይህንን ከእርሷ በመስማቱ እጅግ ተቆጣ፤ በመናቁም ተበሳጨ፤ አሽከሮቹንም ጠርቶ በቤተ መንግሥቱ የታሰሩትን አንበሶች እንዲለቀቅባቸው አዘዘ፡፡ አንበሶቹ ግን ይደሰቱ ነበር፡፡ በኋላም ፊታቸውን ወደ ንጉሡና አገልጋዮቹ በማዞር ሩጠው እስኪደበቁ ድረስ አሳደዷቸው፡፡ ንጉሡ ይበልጥ ነደደው ክርስቲያኖቹ በረሃብ እንዲያልቁ እንዲታሰሩ አዘዘ፡፡ እግዚአብሔርም በአምስተኛው ቀን በብርሃን ቤቱን ሞልቶት የሚበሉትን በመሶብ የሚጠጡትን በጽዋ ከሰማይ አወረደላቸው፡፡ ንጉሡም ይህንን በማየቱ ከዚያ አውጥቶ በእሳት ውስጥም አስገባቸው፡፡ ሠለስቱ ደቂቅን የጠበቀ አምላክ እነርሱንም አዳናቸው፡፡ በሌላም በብዙ መንገድ ሊያጠፋቸው እንደሞከረ ገድሏ ይተርካል፡፡ በመጨረሻም ከአማካሪዎቹ ጋር ተማክሮ በሰይፍ እንዲያልቁ ይወስናሉ፡፡
እያንዳንዳቸውን ተራ በተራ ሲሰይፋቸው ቅድስት አርሴማ ለሚሰየፉት ሁሉ የድል አክሊል ከሰማይ ሲወርድላቸው ትመለከት ስለነበር የእርሷን ተራ በጉጉት ትጠብቀው ነበር፡፡ በመደሰቷም እየጸለየች አይዟችሁ ጽኑ ትላቸው ነበር፡፡
በመጨረሻም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጽናቷን ተመልክቶ ቃል ኪዳን ይገባላታል፡፡ ንጉሡም ሌሎቹን አሰይፎ ሲያበቃ ወደሷ ዞሮ በቁጣ እየጮኸ አንቺን እንደ ባልንጀሮችሽ በቀላሉ አልገልሽም ስቃይሽን አጸናብሻለሁ ብሎ ለአገልጋዮቹ ትእዛዝ በመስጠት አይኗን አስወጥቶ በእጇ ያሲዛታል፤ ጡቷን ያስቆርጣል፤ በኋላም አንገቷን ያሰይፋታል በዚሁ ሁኔታ እናታችን ሰማዕትነትን ተቀበለች፡፡
ይህንን ሁሉ መከራ ስለአምላኳ ስትል እራሷን አሳልፋ የሰጠች ድንቅ ሰማዕት ናት፡፡ ነቢዩ ዳዊት በመዝሙሩ ‘‘ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ’’ (መዝ.) እንዳለ ለእናታችንም የገባላት ቃል ኪዳን ‘‘በእኔ ስም አምነሽ የዚህ ዓለም ተድላና ደስታ ሳያታልልሽ አንገትሽን ለሰይፍ ሰጥተሽ ተሰይፈሻል፤ የሰማዕትነት ተጋድሎ ፈጽመሻልና ስምሽን የጠራ፤ በዓልሽን ያከበረ፤ ዝክርሽን የዘከረ፤ ገድልሽን የጻፈና ያጻፈ፤ የሰማና ያሰማም እስከ ፲፪ ትውልድ ድረስ እምርልሻለሁ’’ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ በዚህም መሠረት በሷ አማላጅነት አምኖ እገዳሟም ሄዶ በጸሎት የተማጸናት ሁሉ ለችግሩ መፍትሄ አግኝቶ እንደሚመለስ እሙን ነው፡፡ የቅድስት አርሴማ ረድኤት በረከት ጸሎትና ምልጃ ከእኛ ጋር ይኑር፡፡ አሜን አሜን አሜን
አሜን የእናታችን በረከቷ ይደርብን!!!!
Friday, May 20, 2011
Saturday, February 12, 2011
መልክዐ አርሴማ ቅድስት(አማርኛ)
መልክዐ አርሴማ ቅድስት(አማርኛ)
በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንድ አምላክ ብልን እናምናለን፡፡ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
ይህንን መጽሃፍ ያነበበ የተረጎመ የሰማ የቅድስት አርሴማ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል፡፡
1-ሰላም ለጽንሰትኪ
በጳጳሳት አለቃ ጸሎት ለመጸነስሽ ሰላምታ ይገባሻል፡፡ በእግዚአብሔር ፈቃድም ከእናትሽ ማህጸን ለመወለድሽ ሰላምታ ይገባሻል፡፡ለዚህ ንግግር መግቻ የሚሆን የምስጋና መብራትን በአንቺ እሾምበት ዘንድ አንደበቴን አስማሚልኝ በጭንቄ ጊዜ ባለቤቱ አንቺ ነሽና፡፡
2-ሰላም ለዝክረ ስምኪ
በቃል ኪዳን መጎናጸፊያ ለተጠቀለለ ስምሽ መታሰቢያ ስላምታ ይገባዋል፡፡ የጥራቱ ህብር ለሚያበራ ጠጉርሽን ሰላምታ ይገባል፡፡ ትዕግሥትን የተሸለምሽ ገድልንም ለተጎናጸፍሽ ቅድስት አርሴማ ሆይ ረቂቅ የሚሆን የኃይልሽ ትርጓሜ መሸከሚያ በአንደበቴና በኔ ቃል ይጻፍ፡፡
3- ሰላም ለርዕሲኪ
ሃይማኖት ሽቱን ለተቀባ ራስሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የማሰተዋል ብርሀንን ተመልቶ ለነበረ መልክሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቅድስት አርሴማ ሆይ ጌታሽ የዕጽ መስቀል ላይ የወደቀ በግን እስከሚያገኝ ድረስ የተረሳ አዳምን በፈለገ ግዜ ከሰማይ ከብልጽግ ወደ ችግር ምድር ወረደ፡፡
4-ሰላም ለቀራንብትኪ
የመልክና የደም ግባት መውደድ ላላቸው ቅንድቦችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ እንደ ብርሃን ክዋክብት ለሚያስደስቱ ዓይኖችሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቅድስት አርሴማ ሆይ ከሐዲስ ቃል ኪዳን ምንጭና ከለመለመ ፈለግ ጋራ ወደ ታመመችና ባህሪይዋ ውሃነት ወዳላት ሥራዬ የሕይወት መድሃኒት ውሃን ካንቺ ዘንድ ይፍሰስልኝ፡፡
5-ሰላም ለአእዛንኪ
የምሰራች ወርቆቹን ለተሸለሙ ጆሮችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡እንደ ሮማን ቅርፊት ቀዮች ለሚሆኑ ጉንጮችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ በደብረ ሲና አስርቱ ቃላት እንዳሉበት ታቦተ ጽዮን ቃል ኪዳን ያለሽ የዕውነት ኃይል ታቦት አርሴማ ሆይ ከይቅርታሽ ደመና የተነሳ የሚፈውስ የአማረ ህይወተ መናን ወደ ተራበ ሆዴ መግቢኝ፡፡
6-ሰላም ለአእናፊኪ
ንጹህ በሚሆን ወርቅ ተነብዩ አፍሽና ከንፈርሽ ጋር አንዱ እንደተመረጠ ሽቱ እቃ ለሚያስደስቱ አፍንጮችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ለተጨነቁና ውሃን ለተጠሙ የበረከት ጠበል አርሴማ ሆይ ከረድኤትሽ ሰማይ የነጠበ ዝናም ኃይልሽና ፍቅርሽ ውሃ በኔ ላይ ይፍሰስ፡፡
7-ሰላም ለአስናንኪ
እንደ እንቁ ለተደረደሩ ጥርሶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡የጌታችንን መስቀል ነገር ለሚናገር ልሳንሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ የሰማእታት ምሰሶ የደካሞች ኃይል የምትሆኝ ቅድስት አርሴማ ሆይ የነበልባልና የእሳት ዲን ስቃይ በአንቺ ጠፋ የታመነ ታሪክሽ እንዲህ ይላልና፡፡
8-ሰላም ለቃልኪ
የተበተነ ልቡናን ለሚሰበስብ ቃልሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ደዌ ኃጢያትን ለሚያድን ሕይወት ትንፋሽሽም ሰላምታ ይገባል፡፡የምስኪኞች ተስፋ የደካሞች አረጋጊ አርሴማ ሆይ የሚያቃጥል እሳትና ከባድ በሚሆን ጨለማ ዘመን ጊዜ በሚጠቅም ቃልኪዳንሽ አድኝኝ፡፡
9-ሰላም ለጉርኤኪ
ምስጋና ወተትን ለጠባ ጉሮሮሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ እንደ ስይፍ ስለት የወርቅ ገንቦን ለተሸለመ አንገትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ልዩ በሚሆን በስላሴ ባህርይና የተዘጋጀ አንድነት ብርሃንን በመቀበል ከሰማዕታት ጋር ያለመ ወንጀል ቅድስት አርሴማ ሆይ ከተቀደሰ ቦታሽ እንዴት አየሽ፡፡
10-ሰላም ለመታከፍትኪ
የስቃይ ቀንበር ለተሸከመ ትከሻሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የስዕልሽ መንበር ለመገረፍ ንግስ ለሆነ ጀርባሽ ሰላምታ ይገባል፡፡በረሃውን ከእረፍት ጋር የሚያለመልም ዝናመ ምህረትን አርሴማ አሳስቢልን፡፡
11-ሰላም ለእንግድአኪ
የዓለም ወርቅን ለጠላ ደረትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የመቅስፍትና የስቃይ መቀመጫ ለሚሆን ብብትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ የመሰናክል ድንጋይ ድርጣድስ በተፈታተነሽ ጊዜ ስለሃይማኖትሽ ያዕቆባዊ መጽሃፍን ትገልጭለት ዘንድ ጣኦታትንም አጠፋሽ ባዕድ አምላክንም ሰበርሽ፡፡
12-ሰላም አአእዳውኪ
የህማማት ወርቅን ለተሸለሙ እጆችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የኃጢያት አለቶችንም ለአጠፋ ክንድሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ ስለፍቅርሽ ልቤ ተመስጧልና ስለነፍሴ ቁስል የጣፈጠ ሽቱን ትቀቢኝ ዘንድ ጥቂት አዘጋጂልኝ፡፡
13-ሰላም ለኳርናዕኪ
የትዕግስት ራስ ትራስ ለሚሆን ክንድሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ሀዲስ የሚሆን ተስፋ አካልን ለሚልክ ክንድሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ የይቅርታ አዳራሽ አርሴማ ሆይ ከወንጌላዊት መቅደስ በምሽት ጊዜ ከብስራታዊ መንበር ውስጥ እንደልመናዬ አገልጋይ ኃይልሽ ይሰዋልኝ፡፡
14-ሰላም ለእራኀኪ
ጸጋ ሀብትን ለሚስጥ መሃል እጅሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የጥበብ መብራቶችንም ለሚሆኑ ጣቶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የቅዱሳን መመኪያ አርሴማ ሆይ እንደ ሰማዕታት አለቃ ጊዮርጊስ የሁሉ ጌጥ ራሶችና አራዊትን እረግጥ ዘንድ የአብ ሰልጣንን ለኔ ላኪልኝ፡፡
15-ሰላም ለአድፋረእዴኪ
ነጭነታቸው ለሚያስደንቁ ጥፍሮቸሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ እንደ ትዕግስት ፏፏቴ ወተት ምንጭ ለሚሆኑ ጡቶችሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቅድስት አርሴማ ሆይ በረድኤትሽና በአንቺ ፍቅር ተደፋፋሪ ይውደቅ የጠላቴ ምክርም ከፊቴ ይበተን በሰማይና በምድር ተመጻድቆብኛልና፡፡
16-ሰላም ለገበዋትኪ
ስቃይን ለተጎናጸፈ ጎኖችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ትርጓሜ እህልን ለተመገበ ሆድሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ አፌ ስምሽን ባመሰገነ ጊዜ በመነሳት ጽኖም የተሰፋሽ ውሃን እስከማገኝ ድረስ በኔ ላይ ይቅርታ ዝናም ይፍሰስልኝ፡፡
17-ሰላም ለልብኪ
ጨለማና በቀልን ለተወ ልብሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ እንደ አዲስ ወንጌል ምንቾች ንጹህ ለሚሆኑ ኩላሊቶችሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቅድስት አርሴማ ሆይ ሶስት ለሚሆኑ የስላሴ ስምን በመታመን በጠራሁሽ ጊዜ በኃይልና በረድኤት ቀን ዳጎን ጠፋ ጣኦቱም ፈረሰ፡፡
18- ሰላም ለህሊናኪ
የጌታ አገዛዝን ለሚያስብ ሕሊናሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ለትሩፋት ሰውነት ጋር አንድ ለሚሆኑ አንጀቶችሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ የጳውሎስ ሰይፍንና የጴጥሮስ አሳብን የተቀበልሽ አርሴማ ሆይ እየቀኑ ታረጋጊኝ ዘንድ የረድኤትሽ ባህሮች በላዬ ላይ ይስፋፉ፡፡
19-ሰላም ለንዋየ ለውስጥኪ
ከርኩሰት ንጹህ ለሚሆን ለውስትሽ ሰውነት ሰላምታ ይገባል፡፡ ሀዲስ የሚሆን ተስፋ ፍሬን ለአፈራ ጅማትሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ የትንቢትና የመጽሃፍ ምንጭ አርሴማ ሆይ በገነት ልቤ ዘወትር በለስ ያገኝ ዘንድ በጠብና በተንኮል ዘመን ጊዜ የፍቅር ውሃን አጠጪኝ፡፡
20- ሰላም ለኀንብርትኪ
ከሆድ መካከል ላይ ለሚኖር ማዕከላዊ መለያ ላለው ኀብርትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የመድኃኒታችን ክርስቶስ ሙሽራ አርሴማ ሆይ ከተወደደ ጌታችን ጋር ሰማያዊ ከሚሆን ሰርግ ቤት ውስጥ በተቀመጥሽ ጊዜ በቃል ኪዳንሽ መክፈቻ ደጃፍን ለኔ ክፈችልኝ፡፡
21-ሰላም ለኃቋኪ
የኀማማት መታጠቂያን ለታጠቀ ወገብሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ቁመትን ለተጎራበቱ መንቶች ብብቶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ መብራትን በአጣን በዚህ ዘመን መቋቋም ለኔ ብርሃን ጥበቃን ታበሪልኝ ዘንድ ከአለም አኩኋን ፈተና አንዲት ነፍሴን እለምንሻለሁኝ፡፡
22-ሰላም ለአብራክኪ
የእጅና የእግር መመላለሻ ከሚገለገልበት ስግደት ጸሎት አዳራሽ ለጉልበቶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ክርስቲያናዊት አርሴማ ሆይ ጥርጥርና ክህደትን የተውሽ ብትሆኝ ከአደባባይ ስቃይን በአቆምሽ ጊዜ ከነጎድጓድና ከመብረቅ ማሰፈራት የተነሳ ምድር ተነዋወጠች፡፡ ቀስተ ደመናም እንደ ምሶሶ ተተከለ፡፡
23-ሰላም ለሰኮናኪ
በአሳላፊ ቤት ለሚያድጥ ተረከዝሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ከገስጋሽ ሰማዕት ቦታ ውስጥ ቀልጣፋ ለሚሆን ለእግርሽ ተረከዝም ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ ደግ ሰው ስምሽን በጠራ ጊዜ በአነሳሲታ ደምሽ የልቡና በድንን ዳሰሽ ዳግመኛም በህይወት ውሃ በደሉን አጥፊ፡፡
24-ሰላም ለአጻብእኪ
የእናሶስላ መነከርን ለለመዱ ነጮች ጥፍሮችሽ ለተሸለሙ ጣቶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ አንቺ አርሴማ ሆይ ከቆንጆ ቤት ምስክርነት ቦታ እንግዳ በሚሆን ረድኤትሽ ወዳጅሽን አድኝኝ የልብ በሽታ ህማም እንዳያስጨንቀኝ፡፡
25-ሰላም ለቆምኪ
የባለሟልነትና የማፈራት ምንጮችን ዘወትር የሚጠጣ የደጋ ዛፍ ለሚመስል ቁመትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ በክፍ ዘመንም ከመውደቅ ደግፊኝ ከድካምም አድኝኝ፡፡ አርሴማ ሆይ የመጽሃፍሽ መቆለፊያን ዕከፍት ዘንድ ስምሽ የልመና ጸሎትን ሆነልኝ፡፡
26-ሰላም ለመልክዕኪ
ደመና ዝሙት የሸፈነው የወንጀለኛ ንጉስ ልብን በገደለ መልክሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ ቅዱስ በሚሆን መስቀል ምልክት አድኝኝ ወደ ምስጋናና ወደ ደስታ የፍቅርሽ ገመድ ልቤን ስቦታልና፡፡
27-ሰላም ለጸአተ ነፍስኪ
ወደ አዘነበለ አንገትሽ በሚያልፍ ሰይፍ ጊዜ ለነፍስሽ መውጣት ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ መስዋዕትን በሚቀበል ጌታሽ ዘንድ የተረፈ ረድኤትሽ በኔ ላይ ይወርድ ዘንድ በከንፈርና በአፍ እለምንሻለሁኝ፡፡ የተቆጠሩ ሞትሽ ይህን ነገር አሳይቶኛል፡፡
28-ሰላም ለበድነ ሥጋኪ
ጨረቃን ለመሰለ ለሥጋሽ በድን ሰላምታ ይገባል፡፡ በምስጋና ወገንተኞች መላዕክት እጅ ለተቀደሰ መገነዝሽም ሰላምታ ይገባል፡፡
ቅድስት አርሴማ ሆይ ከጥልቅ ጥፋት ወደ ውስጥ ከግብጽ ከተማ ጠላቶችን በምስጋና ቃልኪዳንሽና ሙሴ ኃይልሥ ያሰጥማቸው ዘንድ ሰላምታ ይገባል፡፡
29-ሰላም ለመቃብርኪ
ከሰማዕታት ጋር ካረፍሽበት አርማንያ ቦታ ለመቃብርሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ በአርአያና በምሳሌ ከተናገርኩት ክብርሽ የተነሳ የሽንገላ እጅ ያልዳሰሰሽ የመነሳት ዕቃ አርሴማ ሆይ ከከንፈርና አፍ ምሳጋናን ይጥገብ፡፡
30-ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ
በፈጣሪ ቃል ለተመሰገነ ለስጋሽ መፍለስ ሰላምታ ይገባል፡፡ የዚህ አለም ኑሮን ላልፈለገ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ብጽዕት አርሴማ ሆይ ችግርን እንዳላይ ከበረከተ ዕቃሽ መግቢያ ማረስን አልችልምና ጥቂት በረከትሽን ትሰጪኝ ዘንድ እለምንሻለሁኝ፡፡
31-ሰላም ለዘአእረፋ ምሰሌኪ
ከአንቺ ጋር ለአረፉ ለሀያ ሰባቱ ሰማዕታት ሰላምታ ይገባል፡፡ ከብዙ ይቅርታ ጋር እና ቅድስት ከምትሆን ስምሽም ጋራ ሰማቸው ወደ አለበት ቦታ ረድኤታቸው በኔ ላይ ተወርድ ዘንድ አርሴማ ሆይ በሁሉ ዘመንና በሁሉ ዓመታት የሞትና የህማም በሽታ ዳግመኛ አይቅረብ፡፡
32- ሰብሃት ለአብ
ሰራችንን ላሳመረልን ለአብ ምስጋና ይገባል፡፡ ፈጥኖ ለረዳን ለወልድም ምስጋና ይገባል፡፡ ስልጣንን ለሰጠን ለመንፈስ ቅዱስም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቃልኪዳንን የያዝሽ አርሴማ ሆይ የታመነ ምስጋናሽን አነበንባለሁ፡፡ ኃጥአንን ታማልጅ ዘንድ፡፡ የቅድስት አርሴማ አምላክ ሆይ ከነፍስና ከሥጋ መከራ አድነን፡፡ ጠብቀንም፡፡
በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንድ አምላክ ብልን እናምናለን፡፡ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
ይህንን መጽሃፍ ያነበበ የተረጎመ የሰማ የቅድስት አርሴማ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል፡፡
1-ሰላም ለጽንሰትኪ
በጳጳሳት አለቃ ጸሎት ለመጸነስሽ ሰላምታ ይገባሻል፡፡ በእግዚአብሔር ፈቃድም ከእናትሽ ማህጸን ለመወለድሽ ሰላምታ ይገባሻል፡፡ለዚህ ንግግር መግቻ የሚሆን የምስጋና መብራትን በአንቺ እሾምበት ዘንድ አንደበቴን አስማሚልኝ በጭንቄ ጊዜ ባለቤቱ አንቺ ነሽና፡፡
2-ሰላም ለዝክረ ስምኪ
በቃል ኪዳን መጎናጸፊያ ለተጠቀለለ ስምሽ መታሰቢያ ስላምታ ይገባዋል፡፡ የጥራቱ ህብር ለሚያበራ ጠጉርሽን ሰላምታ ይገባል፡፡ ትዕግሥትን የተሸለምሽ ገድልንም ለተጎናጸፍሽ ቅድስት አርሴማ ሆይ ረቂቅ የሚሆን የኃይልሽ ትርጓሜ መሸከሚያ በአንደበቴና በኔ ቃል ይጻፍ፡፡
3- ሰላም ለርዕሲኪ
ሃይማኖት ሽቱን ለተቀባ ራስሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የማሰተዋል ብርሀንን ተመልቶ ለነበረ መልክሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቅድስት አርሴማ ሆይ ጌታሽ የዕጽ መስቀል ላይ የወደቀ በግን እስከሚያገኝ ድረስ የተረሳ አዳምን በፈለገ ግዜ ከሰማይ ከብልጽግ ወደ ችግር ምድር ወረደ፡፡
4-ሰላም ለቀራንብትኪ
የመልክና የደም ግባት መውደድ ላላቸው ቅንድቦችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ እንደ ብርሃን ክዋክብት ለሚያስደስቱ ዓይኖችሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቅድስት አርሴማ ሆይ ከሐዲስ ቃል ኪዳን ምንጭና ከለመለመ ፈለግ ጋራ ወደ ታመመችና ባህሪይዋ ውሃነት ወዳላት ሥራዬ የሕይወት መድሃኒት ውሃን ካንቺ ዘንድ ይፍሰስልኝ፡፡
5-ሰላም ለአእዛንኪ
የምሰራች ወርቆቹን ለተሸለሙ ጆሮችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡እንደ ሮማን ቅርፊት ቀዮች ለሚሆኑ ጉንጮችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ በደብረ ሲና አስርቱ ቃላት እንዳሉበት ታቦተ ጽዮን ቃል ኪዳን ያለሽ የዕውነት ኃይል ታቦት አርሴማ ሆይ ከይቅርታሽ ደመና የተነሳ የሚፈውስ የአማረ ህይወተ መናን ወደ ተራበ ሆዴ መግቢኝ፡፡
6-ሰላም ለአእናፊኪ
ንጹህ በሚሆን ወርቅ ተነብዩ አፍሽና ከንፈርሽ ጋር አንዱ እንደተመረጠ ሽቱ እቃ ለሚያስደስቱ አፍንጮችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ለተጨነቁና ውሃን ለተጠሙ የበረከት ጠበል አርሴማ ሆይ ከረድኤትሽ ሰማይ የነጠበ ዝናም ኃይልሽና ፍቅርሽ ውሃ በኔ ላይ ይፍሰስ፡፡
7-ሰላም ለአስናንኪ
እንደ እንቁ ለተደረደሩ ጥርሶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡የጌታችንን መስቀል ነገር ለሚናገር ልሳንሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ የሰማእታት ምሰሶ የደካሞች ኃይል የምትሆኝ ቅድስት አርሴማ ሆይ የነበልባልና የእሳት ዲን ስቃይ በአንቺ ጠፋ የታመነ ታሪክሽ እንዲህ ይላልና፡፡
8-ሰላም ለቃልኪ
የተበተነ ልቡናን ለሚሰበስብ ቃልሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ደዌ ኃጢያትን ለሚያድን ሕይወት ትንፋሽሽም ሰላምታ ይገባል፡፡የምስኪኞች ተስፋ የደካሞች አረጋጊ አርሴማ ሆይ የሚያቃጥል እሳትና ከባድ በሚሆን ጨለማ ዘመን ጊዜ በሚጠቅም ቃልኪዳንሽ አድኝኝ፡፡
9-ሰላም ለጉርኤኪ
ምስጋና ወተትን ለጠባ ጉሮሮሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ እንደ ስይፍ ስለት የወርቅ ገንቦን ለተሸለመ አንገትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ልዩ በሚሆን በስላሴ ባህርይና የተዘጋጀ አንድነት ብርሃንን በመቀበል ከሰማዕታት ጋር ያለመ ወንጀል ቅድስት አርሴማ ሆይ ከተቀደሰ ቦታሽ እንዴት አየሽ፡፡
10-ሰላም ለመታከፍትኪ
የስቃይ ቀንበር ለተሸከመ ትከሻሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የስዕልሽ መንበር ለመገረፍ ንግስ ለሆነ ጀርባሽ ሰላምታ ይገባል፡፡በረሃውን ከእረፍት ጋር የሚያለመልም ዝናመ ምህረትን አርሴማ አሳስቢልን፡፡
11-ሰላም ለእንግድአኪ
የዓለም ወርቅን ለጠላ ደረትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የመቅስፍትና የስቃይ መቀመጫ ለሚሆን ብብትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ የመሰናክል ድንጋይ ድርጣድስ በተፈታተነሽ ጊዜ ስለሃይማኖትሽ ያዕቆባዊ መጽሃፍን ትገልጭለት ዘንድ ጣኦታትንም አጠፋሽ ባዕድ አምላክንም ሰበርሽ፡፡
12-ሰላም አአእዳውኪ
የህማማት ወርቅን ለተሸለሙ እጆችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የኃጢያት አለቶችንም ለአጠፋ ክንድሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ ስለፍቅርሽ ልቤ ተመስጧልና ስለነፍሴ ቁስል የጣፈጠ ሽቱን ትቀቢኝ ዘንድ ጥቂት አዘጋጂልኝ፡፡
13-ሰላም ለኳርናዕኪ
የትዕግስት ራስ ትራስ ለሚሆን ክንድሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ሀዲስ የሚሆን ተስፋ አካልን ለሚልክ ክንድሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ የይቅርታ አዳራሽ አርሴማ ሆይ ከወንጌላዊት መቅደስ በምሽት ጊዜ ከብስራታዊ መንበር ውስጥ እንደልመናዬ አገልጋይ ኃይልሽ ይሰዋልኝ፡፡
14-ሰላም ለእራኀኪ
ጸጋ ሀብትን ለሚስጥ መሃል እጅሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የጥበብ መብራቶችንም ለሚሆኑ ጣቶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የቅዱሳን መመኪያ አርሴማ ሆይ እንደ ሰማዕታት አለቃ ጊዮርጊስ የሁሉ ጌጥ ራሶችና አራዊትን እረግጥ ዘንድ የአብ ሰልጣንን ለኔ ላኪልኝ፡፡
15-ሰላም ለአድፋረእዴኪ
ነጭነታቸው ለሚያስደንቁ ጥፍሮቸሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ እንደ ትዕግስት ፏፏቴ ወተት ምንጭ ለሚሆኑ ጡቶችሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቅድስት አርሴማ ሆይ በረድኤትሽና በአንቺ ፍቅር ተደፋፋሪ ይውደቅ የጠላቴ ምክርም ከፊቴ ይበተን በሰማይና በምድር ተመጻድቆብኛልና፡፡
16-ሰላም ለገበዋትኪ
ስቃይን ለተጎናጸፈ ጎኖችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ትርጓሜ እህልን ለተመገበ ሆድሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ አፌ ስምሽን ባመሰገነ ጊዜ በመነሳት ጽኖም የተሰፋሽ ውሃን እስከማገኝ ድረስ በኔ ላይ ይቅርታ ዝናም ይፍሰስልኝ፡፡
17-ሰላም ለልብኪ
ጨለማና በቀልን ለተወ ልብሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ እንደ አዲስ ወንጌል ምንቾች ንጹህ ለሚሆኑ ኩላሊቶችሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቅድስት አርሴማ ሆይ ሶስት ለሚሆኑ የስላሴ ስምን በመታመን በጠራሁሽ ጊዜ በኃይልና በረድኤት ቀን ዳጎን ጠፋ ጣኦቱም ፈረሰ፡፡
18- ሰላም ለህሊናኪ
የጌታ አገዛዝን ለሚያስብ ሕሊናሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ለትሩፋት ሰውነት ጋር አንድ ለሚሆኑ አንጀቶችሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ የጳውሎስ ሰይፍንና የጴጥሮስ አሳብን የተቀበልሽ አርሴማ ሆይ እየቀኑ ታረጋጊኝ ዘንድ የረድኤትሽ ባህሮች በላዬ ላይ ይስፋፉ፡፡
19-ሰላም ለንዋየ ለውስጥኪ
ከርኩሰት ንጹህ ለሚሆን ለውስትሽ ሰውነት ሰላምታ ይገባል፡፡ ሀዲስ የሚሆን ተስፋ ፍሬን ለአፈራ ጅማትሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ የትንቢትና የመጽሃፍ ምንጭ አርሴማ ሆይ በገነት ልቤ ዘወትር በለስ ያገኝ ዘንድ በጠብና በተንኮል ዘመን ጊዜ የፍቅር ውሃን አጠጪኝ፡፡
20- ሰላም ለኀንብርትኪ
ከሆድ መካከል ላይ ለሚኖር ማዕከላዊ መለያ ላለው ኀብርትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የመድኃኒታችን ክርስቶስ ሙሽራ አርሴማ ሆይ ከተወደደ ጌታችን ጋር ሰማያዊ ከሚሆን ሰርግ ቤት ውስጥ በተቀመጥሽ ጊዜ በቃል ኪዳንሽ መክፈቻ ደጃፍን ለኔ ክፈችልኝ፡፡
21-ሰላም ለኃቋኪ
የኀማማት መታጠቂያን ለታጠቀ ወገብሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ቁመትን ለተጎራበቱ መንቶች ብብቶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ መብራትን በአጣን በዚህ ዘመን መቋቋም ለኔ ብርሃን ጥበቃን ታበሪልኝ ዘንድ ከአለም አኩኋን ፈተና አንዲት ነፍሴን እለምንሻለሁኝ፡፡
22-ሰላም ለአብራክኪ
የእጅና የእግር መመላለሻ ከሚገለገልበት ስግደት ጸሎት አዳራሽ ለጉልበቶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ክርስቲያናዊት አርሴማ ሆይ ጥርጥርና ክህደትን የተውሽ ብትሆኝ ከአደባባይ ስቃይን በአቆምሽ ጊዜ ከነጎድጓድና ከመብረቅ ማሰፈራት የተነሳ ምድር ተነዋወጠች፡፡ ቀስተ ደመናም እንደ ምሶሶ ተተከለ፡፡
23-ሰላም ለሰኮናኪ
በአሳላፊ ቤት ለሚያድጥ ተረከዝሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ከገስጋሽ ሰማዕት ቦታ ውስጥ ቀልጣፋ ለሚሆን ለእግርሽ ተረከዝም ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ ደግ ሰው ስምሽን በጠራ ጊዜ በአነሳሲታ ደምሽ የልቡና በድንን ዳሰሽ ዳግመኛም በህይወት ውሃ በደሉን አጥፊ፡፡
24-ሰላም ለአጻብእኪ
የእናሶስላ መነከርን ለለመዱ ነጮች ጥፍሮችሽ ለተሸለሙ ጣቶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ አንቺ አርሴማ ሆይ ከቆንጆ ቤት ምስክርነት ቦታ እንግዳ በሚሆን ረድኤትሽ ወዳጅሽን አድኝኝ የልብ በሽታ ህማም እንዳያስጨንቀኝ፡፡
25-ሰላም ለቆምኪ
የባለሟልነትና የማፈራት ምንጮችን ዘወትር የሚጠጣ የደጋ ዛፍ ለሚመስል ቁመትሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ በክፍ ዘመንም ከመውደቅ ደግፊኝ ከድካምም አድኝኝ፡፡ አርሴማ ሆይ የመጽሃፍሽ መቆለፊያን ዕከፍት ዘንድ ስምሽ የልመና ጸሎትን ሆነልኝ፡፡
26-ሰላም ለመልክዕኪ
ደመና ዝሙት የሸፈነው የወንጀለኛ ንጉስ ልብን በገደለ መልክሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ ቅዱስ በሚሆን መስቀል ምልክት አድኝኝ ወደ ምስጋናና ወደ ደስታ የፍቅርሽ ገመድ ልቤን ስቦታልና፡፡
27-ሰላም ለጸአተ ነፍስኪ
ወደ አዘነበለ አንገትሽ በሚያልፍ ሰይፍ ጊዜ ለነፍስሽ መውጣት ሰላምታ ይገባል፡፡ አርሴማ ሆይ መስዋዕትን በሚቀበል ጌታሽ ዘንድ የተረፈ ረድኤትሽ በኔ ላይ ይወርድ ዘንድ በከንፈርና በአፍ እለምንሻለሁኝ፡፡ የተቆጠሩ ሞትሽ ይህን ነገር አሳይቶኛል፡፡
28-ሰላም ለበድነ ሥጋኪ
ጨረቃን ለመሰለ ለሥጋሽ በድን ሰላምታ ይገባል፡፡ በምስጋና ወገንተኞች መላዕክት እጅ ለተቀደሰ መገነዝሽም ሰላምታ ይገባል፡፡
ቅድስት አርሴማ ሆይ ከጥልቅ ጥፋት ወደ ውስጥ ከግብጽ ከተማ ጠላቶችን በምስጋና ቃልኪዳንሽና ሙሴ ኃይልሥ ያሰጥማቸው ዘንድ ሰላምታ ይገባል፡፡
29-ሰላም ለመቃብርኪ
ከሰማዕታት ጋር ካረፍሽበት አርማንያ ቦታ ለመቃብርሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ በአርአያና በምሳሌ ከተናገርኩት ክብርሽ የተነሳ የሽንገላ እጅ ያልዳሰሰሽ የመነሳት ዕቃ አርሴማ ሆይ ከከንፈርና አፍ ምሳጋናን ይጥገብ፡፡
30-ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ
በፈጣሪ ቃል ለተመሰገነ ለስጋሽ መፍለስ ሰላምታ ይገባል፡፡ የዚህ አለም ኑሮን ላልፈለገ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ ብጽዕት አርሴማ ሆይ ችግርን እንዳላይ ከበረከተ ዕቃሽ መግቢያ ማረስን አልችልምና ጥቂት በረከትሽን ትሰጪኝ ዘንድ እለምንሻለሁኝ፡፡
31-ሰላም ለዘአእረፋ ምሰሌኪ
ከአንቺ ጋር ለአረፉ ለሀያ ሰባቱ ሰማዕታት ሰላምታ ይገባል፡፡ ከብዙ ይቅርታ ጋር እና ቅድስት ከምትሆን ስምሽም ጋራ ሰማቸው ወደ አለበት ቦታ ረድኤታቸው በኔ ላይ ተወርድ ዘንድ አርሴማ ሆይ በሁሉ ዘመንና በሁሉ ዓመታት የሞትና የህማም በሽታ ዳግመኛ አይቅረብ፡፡
32- ሰብሃት ለአብ
ሰራችንን ላሳመረልን ለአብ ምስጋና ይገባል፡፡ ፈጥኖ ለረዳን ለወልድም ምስጋና ይገባል፡፡ ስልጣንን ለሰጠን ለመንፈስ ቅዱስም ሰላምታ ይገባል፡፡ ቃልኪዳንን የያዝሽ አርሴማ ሆይ የታመነ ምስጋናሽን አነበንባለሁ፡፡ ኃጥአንን ታማልጅ ዘንድ፡፡ የቅድስት አርሴማ አምላክ ሆይ ከነፍስና ከሥጋ መከራ አድነን፡፡ ጠብቀንም፡፡
Friday, February 11, 2011
ጾመ ነነዌ
የነነዌ ጾም ከሰባቱ የቤተክርስቲያን አጽዋማት አንዱና የዐቢይ ጾም ማዘጋጃ ደወል ነው፡፡ ይህ የነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ በቤተክርስቲያናችን በጣም ታላቅ ዋጋ ያለውና የራሱ መዝሙር የሚዘመርለት፣ ቅዳሴ የሚቀደስበት ታላቅ መታሰቢያ ያለው ታሪክ ነው፡፡ ራሱ ጌታችንም የነዌ ሰዎችን የንስሐ ታሪክ በመጥቀስ አይሁድን ገስጾበታል፤ በፍርድ ቀንም በዚያ ትውልድ ዘንድ እንደሚፈርዱበት ተናግሯል፡፡ ይህም የሆነበት የነነዌ ሰዎች ደስ የሚያሰኝ የንስሐ ታሪክ ስላላቸው ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ይህን አስደሳች የንስሐ ታሪክ በጾመ ነነዌ ከሚነበቡ የቅዳሴ ምንባባት አንጻር ለመመርመር እንሞከራለን፡፡
ኃጢአት ከእግዚአብሔር መለየት እንደሆን ሁሉ ንስሐ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው፡፡ በዚህ ከእግዚአብሔር ሊለዩ የሚችሉ ብዙ ፈተናዎች ባለቡት ዓለም እስካለን ድረስ ሕይወታችን ሁሉ የንስሐ ጊዜ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ከሁሉም ጊዜ በተለየ ወደ እግዚአብሔር የምንመለስባቸው የጾም ወቅቶች ሲሆኑ ከእነዚህም ታላቁና ዋነኛው ዐቢይ ጾም ነው፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በዐቢይ ጾም ከእያንዳንዱ ምእመን ልቦና የንስሐ ፍሬን ትፈልጋለች፤ ያለትንሣኤ ልቦና /ንስሐ/ የክርስቶስን ትንሣኤ በእውነትና በደስታ ማክበር አይቻልምና፡፡ ለመሆኑ ከንስሐ የሚያሰናክሉን ነገሮች ምን ምን ናቸው? የነነዌ ሰዎች ታሪክ ስለዚህ ምን ያስተምረናል?
1. ቅንጦትን መውደድ
ምንም እንኳን በደፈናው ገንዘብ የኃጢአት ምንጭ ነው ባንልም እንደ ወንጌል ትእዛዝ በክርስቲያናዊ መንገድ ካልተያዘ ግን እግዚአብሔርን ሊያስረሳና የኃጢአት ማስፈጸሚያና ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ ብዙ ጊዜም ገንዘብና ባለጸግነት ከእግዚአብሔር በመለየታችን ያጣነውን ሰላምና ደስታ ለማግኘት ተስፋ የምንጥልበት ጣኦት ሆኖ ሊቀየር ይችላል፡፡ በሀብታችን በምናገኘው ጊዜያዊ ደስታና ሰላም ዘላለማዊውንና ፍጹምን የእግዚአብሔር ስጦታ መፈለግ፣ ወደ እግዚአብሔር መመለስን መናፈቅ ልናቆም እንችላለን፡፡ በዚህ መልኩ ብልጽግና ከንስሐ የሚያሰናክል ወጥመድ ይሆናል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሀብት እንኳ ቢሰጠን ለተቸገረ በመመጽወት፣ ልጆቻችን በክርስቲያናዊ መንገድ በማሳደግ፣ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በማፋጠን የእውነተኛ ደስታና የጽድቅ መንገድ እንድናደርገው እንጂ እግዚአብሔርን የተጠማች ነፍሳችንን ጥሪዋን በማደናቀፍና ጩኸቷን በማፈን በሥጋ ድሎት ውስጥ የምንደበቅበት መሣሪያ እንድናደረገው አይደለም፡፡ ለ«ታላቂቷ ከተማ» ነነዌም የጥፋት መንገድ የሆናት በብልጽገናዋና በታላቅነቷ እግዚአብሔርን ረስታ የኃጢአት ከተማ መሆኗ ነው፡፡ በነቢዩ በዮናስ ታሪክ ውስጥ ገንዘብ ለዮናስ ከእግዚአብሔር የመከለያ መሣሪያ ሲሆን እናገኘዋልን፡፡ «. .. ከእግዚአብሔርም ፊት ኮብልሎ ከእነርሱ ጋር ወደ ተርሴስ ይሔድ ዘንድ ዋጋ ሰጥቶ ወደ እርሷ /ወደ መርከቧ/ ገባ» እንዲል /ዮና፤1-3/፡፡
በዚህ ሰዓት ለዮናስ ገንዘብ ባይኖረው ይሻል ነበር፡፡ እኛም ቢሆን ከንስሐ የሚመልስ፣ ለኃጢአት መሣሪያ የሚሆን ሀብት ከሚኖረን በድኅነት ብንኖር ይሻለናል፡፡ ምንም እንኳ በቤተክርስቲያናችን ትውፊት ዐቢይ ጾም አብዝተን የምንጸልይበት፣ በጾም በስግደትና በምጽዋት ልናሳልፈው የሚገባ ወቅት ቢሆንም ፤ አሁን አሁን ግን ገንዘብ ማግበስበሻ እየሆነ እንደሆነ እናያለን፡፡ በመሠረቱ በጾም ወቅት ከሆዳችን የምንቀንሰው ገንዘብ እንድናጠራቅመው ሳይሆን እንድንመጸወተው የሚገባ ነው፡፡ ለማጠራቀምማ የማያምኑ ሰዎችስ ምግብ ይቀንሱ የለ? ለዚህ ነው በነነዌ ጾም በመጀመሪያው ቀን /ሰኞ/ የሚነበበው የቅዱስ ያዕቆብ መልእክት «አሁንም እናንተ ባለ ጠጎች ስለሚደርስባችሁ ጭንቅ ዋይ ዋይ እያላችሁ አልቅሱ፡፡ ሀብታችሁ ተበላሽቷል፣ ልብሳችሁም በብል ተበልቷ፡፡ ወርቃችሁም ብራችሁም ዝጓል፤ ዝገቱም ምስክር ይሆንባችኋል፤ ሥጋችሁንም እንደ እሳት ይበላል፡፡ ለኋለኛው ቀን መዝገብን አከማችታችኋል፡፡ እነሆ እርሻሁን ያጨዱት የሠራተኞች ደመወዝ በእናንተ ተቀምቶ ይጮኻል፣የአጫጆችም ድምፅ ወደ ጌታ ጸባዖት ጆሮ ገብቷል፡፡ በምድር ላይ ተቀማጥላችኋል፤ በሴሰኝነትም ኖራችኋል፤ ለእርድ ቀን እንደሚወፍር ልባችሁን አወፍራችኋል፡፡» በማለት አስፈሪ ተግሳጽ የሚያስተላልፈው፡፡ ስለዚህ በዐቢይ ጾም አብዝተን የምንመጸውትበት፣ ከእግዚአብሔር የሆነውን ስጦታ የምንፈልግበት፣ የንስሐ ጊዜ ሊሆን ይገባል፡፡2. ለኃጢአት ሌላ ተጠያቂ መፈለግ
ሌላው ከንስሐ ሲያርቀን የሚገኘው ምክንያት በሰዎች መፍረድ ነው፡፡ በሰዎች የሚፈርድ ሰው ራሱን የሚያጸድቅ ነው፡፡ ራሱን ያጸደቀ ደግሞ ንስሐ መግባትና ከኃጢአት መመለስ ዳገት ይሆንበታል፡፡ ከነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ ውስጥ ለንስሐ በጣም አስቸጋሪ የነበረው ነቢዩ ዮናስ ነው፡፡ መርከበኞቹና የነነዌ ሰዎች በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ወደ እግዚአብሔር ሲመለሱ ዮናስ ግን ከታሪኩ መጀመሪያ እስከ መጨረሻዋ ጊዜ ድረስ በእግዚአብሔር ያጉረመርም ነበር፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ከእግዚአብሔር መኮብለሉና የነነዌ ሰዎችን ድኅነት መቃወሙን እንደ ስህተት እንጂ እንደራሱ ስህተት አለመቁ ጠሩ ነው፡፡ ለዚህ ነበር ከእግዚአብሔር ኮብልሎ ሲሔድ እንኳ ምንም ዓይነት ጭንቀት ሳይሰማው «በከባድ እንቅልፍ» ተኝቶ የነበረው /ዮና.1-5/፡፡ በተመሳሳይ መልኩ አንዳንድ ሰዎች ለራሳቸው ኃጢአት እግዚአብሔርን ተጠያቂ ሲያደርጉ ሌሎች ደግሞ ሰዎችን ተጠያቂ ያደርጋሉ፡፡ በዚህም በራሳቸው ከመፍረድ ይልቅ በሰዎች መፍረድ ይጀምራሉ፤ ወይም የኃጢአታቸው ምክንያት እግዚአብሔርን አድርገው ይገኛሉ፡፡ ነቢዩ ዮናስ የራሱን ክብር ፈላጊነት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ምሕረት የኃጢአቱ ምክንያት ማድረጉ የሚያስገርም ነው፡፡ ይህም ለብዙ ጊዜ ከንስሐ እንዳዘገየው ከታሪኩ እንማራለን፡፡ በተቃራኒው ለንስሐ ቅርብ የሆኑት መርከበኞች በዮናስ ላይ ለመፍረድ ምን ያህል እንደተጨነቁ ስናይ ቀድሞውኑ በዮናስ አለመታዘዝ ምክንያም ቢሆን እግዚአብሔር ወደ ንስሐ ሊመልሳቸው የፈለገ ይህን አይቶ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡3. የእግዚአብሔርን ተግሳጽ አለመቀበል
በነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ሰዎችን ሲገስጽ እንመለከታለን፡፡ ነቢዩ ዮናስን በማዕበል፣ ወደባሕር እንዲወረወር በማድረግ፣ አሳ አንበሪ እንዲውጠው በማድረግእግዚአብሔር ወደ ትክክለኛ መንገዱ ሊመልሰው ቢጥርም በዚህ ሁሉ ሊመለስ አልቻለም፤ ከአሳ አንበሪ አፍ ወጥቶ ሔዶ ቢሰብክም እግዚአብሔር ይቅር ሲላቸው ግን በእግዚአብሔር ላይ ማጉረምረም ጀምሯልና፡፡ ድሮም ቢሆን በፍርሃት እንጂ ስህተቱን ተቀብሎ አልነበረም ወደ ነነዌ ሔዶ የሰበከው፡፡ ግዕዛን የሌላቸው ፍጥረታት /ነፋስ፣ አሳ አንበሪ፣ ትል፣ ፀሐይ/ እንዴት እንደሚታዘዙለት እርሱ ግን ታላቅ ነቢይ ሲሆን አልታዘዝም ማለቱን በማሳየትም ገስጾታል፡፡ በመጨረሻም ለንስሐ በቅቷል፡፡ መርከበኞቹም በመርከባቸው ላይ የተነሣው ማዕበል ተግሳጽ ሆኗቸው ወደ ንስሐ ተልሰዋል፡፡ ከዘላለም ሕይወት እንዳንለይ አጥብቆ የሚፈልገው እግዚአብሔር ልዩ ልዩ መከራዎችንም በማምጣት ወደ ንስሐ እንድንመለስ ያደርጋል፡፡ ለዚህ ተግሳጽ ግን በትክክለኛ ወይም በተሳሳተ መንገድ መልስ ልንሰጥ እንችላለን፡፡ ካወቅንባቸውና ከተጠቀምንባቸው ችግሮችና መከራዎች ወደንስሐ የሚመሩ መንገዶች ናቸው፡፡ የነነዌ ታሪክም የሚነግረን ይህንኑ ነው፡፡ በነነዌ ጾም በቅዳሴ የሚነበቡት የሚከተሉት ምንባባትም በአጽንኦት የሚገልጹት ይህንኑ ነው፡፡ምስባክ:- «ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በላዬ አለፈ፡፡
እግዚአብሔር በቀን ቸርነቱን ያዛል በሌሊትም ዝማሬው በእኔ ዘንድ ይሆናል
የእኔ ስዕለት ለሕይወቴ አምላክ ነው፡፡» /መዝ.41-7-8/መልእክት:- «. . . ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል. . .» /ሐዋ.14-22/፡፡
በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ አሳዛኙ ነገር ሰው ካለፈ ሕይወቱ አለመማሩ ነው፡፡ በነቢዩ በዮናስ ታሪክም የምናገኘው ይህንኑ ነው፡፡ እግዚአብሔር የተሳፈረበትን መርከብ ካናወጠ፣ ዮናስ በአሳ አንበሪ እንዲዋጥ ካደረገ በኋላ እንኳ እግዚአብሔር በነነዌ ሰዎች ላይ ያሳየው ምሕረት ዮናስ ሞትን እስኪመኝ ድረስ እንዲያዝንና በእግዚአብሔር ላይ እንዲያጉረመርም አድርጎታልና፡፡ በእኛም ሕይወት ተመሳሳይ ተግሳጻት ከእግዚአብሔር ዘንድ ቢመጣም ከኃጢአት ባለመመለስ ከዮናስ ያልተለየ መልስ ነው የምንሰጠው፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ራሳችንን የምናይበት፣ በሕይወታችን ያደረጋቸውን የእግዚአብሔር ሥራዎች የምንመረምርበት፣ በውስጣችን ያደፈጡትን አውሬዎች የምናድንበት የተረጋጋና ሰፋ ያለ ጊዜ ስለሌለን ነው፡፡ ይህን አጥብቃ የተረዳችው ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በልዩ ልዩ መንገድ የሚጠራንን የእግዚአብሔር ድምፅ የምናዳምጥበት፣ በመልካም ምክንያቶች የተሸፈኑ ነገር ግን መልካም ያልሆኑና መልካም ልንሠራበት የምንችለውን የሕይወት ጊዜዎችን የሚያቃጥሉ ከንቱ ምኞቶቻችን፣ የማይጨበጡና የማይደረስባቸው «ክፉ ተስፋዎቻችን» ሁሉ የምንመረምርበት፣ መልካሟንና እውነተኛዋን ነገር ግን አስቸጋሪዋንና ጠባቧን የሕይወት መንገዳችን አጉልተን «የምናስምርበት» ሰፋ ያለ ጊዜ ሰጥታናለች፤ ይህም ዐቢይ ጾም ነው፡፡ በዚህ ጊዜ በአግባቡ ከተጠቀምንበትም የዚህን አስቸጋሪና አወናባጅ ዓለም በድል የተወጡ ሰዎች የሚያዩትን የዘለዓለማዊን ሕይወት «ቀብድ» የትንሣኤውን ብርሃን እናያለን፡፡ ዐቢይ ጾምን እንደሚገባ ያላሳለፈ ክርስቲያን ግን የትንሣኤን ድግስ በልቶ ሆዱን ይሞላ እንደሆነ እንጂ የትንሣኤን ታላቅ ደስታ መቅመስ አይችልም፡፡ ስለዚህም ዐቢይ ጾም ለክርስቲያን ታላቅ ስጦታ መሆኑን ልናውቅ ይገባል፡፡ ለዚህም ነው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ስለጾም በጻፉት መጽሐፋቸው «በዐቢይ ጾም ሕይወቱን ያልቀየረ ክርስቲያን በሌሎች አጽዋማት ይቀይራል ማለት ይከብዳል» በማለት የጻፉት፡፡4. ክፉ እኔነት
በዮናስ ታሪክ ውስጥ ከብዙ የዮናስ ስህተቶች ጀርባ የነበረውና ንስሐውን ያዘገየበት ታላቁ መሰናከል ክፉ እኔነት ነው፡፡ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ የነነዌ ሰዎችን ድኀነት ሳይሆን የራሱን ክብር እንዲመለከት ያደረገው በዮናስ ሕይወት ውስጥ በጥልቅ የተተከለ ክፉ እኔነቱ ነው፡፡ በዚያ ሁሉ ታሪክ ውስጥ በርግጥም ዮናስ ስለራሱ እንጂ ስለሰዎች ሲያስብ አልታየም፡፡ ነቢዩ ዮናስ «እኔ ሐሰተኛ ነቢይ ከምባል የነነዌ ሰዎች መጥፋት ይሻላል»«የዮናስ አምላክ ቃሉን ይቀይራል ከምባል የነነዌ ሰዎች ይጥፉ» ብሎ ያስብ እንጂ እግዚአብሔር ግን አላለም፡፡ አመድና ትቢያ የሆነው የሰው ልጅ ስለክብሩ ሲጨነቅ ክብር የባሕሪዩ የሆነ ሩህሩህ አምላክ ግን ማንም እንዲጠፋ አልፈቀደም፡፡ በርግጥ የነነዌ ሰዎች በመዳናቸው የዮናስም የእግዚአብሔርም ቃለ አልታበለም፡፡ ዮናስ «ነነዌ በሦስት ቀን ውስጥ ትጠፋለች» ብሎ ሰበከ፡፡ አመጸኛዋ ነነዌ ግን በቁጣ እሳት ከመጥፋቷ በፊት በንስሐ ራሷን አዋረደች፡፡ በዚያን ጊዜ ነነዌ በንስሐ አዲስ ፍጥረት የሆነች፣ እግዚአብሔር የሚያጠፋት ሳትሆን የሚወዳት ሌላ ነነዌ ሆነች፡፡ ዮናስ ሆይ በንስሐ የታደሰችው ነነዌ የእግዚአብሔርቅን ፍርድ እንደማያጠፋስ ለምን አላሰብክም? ታላቁ የእግዚአብሔር ነቢይ ሆይ ንስሐ የገባችዋን ነነዌን ማጥፋት አምላክህን አያስነቅፈውምን? በነቢዩ በዮናስ ውስጥ ያለው እኔነቱ በርግጥምእግዚአብሔርንም፣ የነነዌ ሰዎችንም እንዳያስብ መጋረጃ ሆኖበት ነበር፡፡ይህን ሁሉ የሕይወታችን ውጥንቅጥ እንመረምርበት ዘንድ ታላቁ የቤተክርስቲያን ስጦታ ዐቢይ ጾም እነሆ፡፡
የእውነተኛ ንስሐ ውጤቶች በነነዌ ሰዎች ታሪክ
5. የዘላለም ሕይወት ተስፋ
ነነዌ የጥፋት ፍርድ ከተፈረደባት በኋላ የመኖር ተስፋ የተሰጣት ከተማ ናት፡፡ በሌላ አነጋገር ነነዌ ሞታ የተነሣች ከተማ ናት ማለት ይቻላል፡፡ ነቢዩ ዮናስም ወደ ባሕር ከተጣለ፣ በአሳ አንበሪ ሆድ ውስጥ ካደረ በኋላ የመኖር ተስፋ የተሰጠው ሰው ነው፡፡ መርከበኞችም መርከባቸው በማዕበል ከተመታች በኋላ፣ ማዕበሉ ካሸነፋቸው በኋላ በእግዚአብሔር ምሕረት ሌላ የመኖር ተስፋ የተሰጣቸው ሰዎች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የነነዌ ታሪክ የተስፋ ታሪክ ነው፡፡ንስሐም በኃጢአት ከሞቱ በኋላ እንደገና የመኖር ተስፋ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች የዘለዓለም ሕይወትን ተስፋ ማድረግ ይከብዳቸዋል፤ ለዚህም ምክንያቱ በንስሐ አለመኖራቸው ነው፡፡ ሰው ያላየውን ነገር እንዴት ይናፍቃል? የማያውቀውን ነገርስ እንዴት ተስፋ ያደርጋል? በንስሐ የሚኖር ሰው ግን የዘለዓለም ሕይወት ቀብድ የሆነ ትንሣኤ ልቦናን ይነሣልና የዘለዓለም ሕይወትን በተስፋ ይናፈቃሉ፡፡ ዐቢይ ጾምንም በንስሐና ራስን በመመርመር ያሳለፈ ሰው በትንሣኤው ትንሣኤን ይቀምሳልና ዘለዓለማዊውን ትንሣኤ በተሰፋ ይናፍቃል፡፡
በነነዌ ጾም የሚነበቡ የቅዳሴ ምንባባትም ይህን እንደሚከተለው ይገልጻሉ፡-
«. . . ትዕግሥትም ፈተናን፣ ፈተናም ተስፋን እንዲያደርግ እያወቅን በመከራችን ደግሞ እንመካለን፡፡ በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም፡፡» /ሮሜ.5-4-5/፡፡6. በእግዚአብሔር ዘንድ መከበር
በንስሐ የተመለሰችው ነነዌ በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ ከብራለች፡፡ የነነዌ ሰዎች ንስሐ በማይገቡ ዘንድ በትውልዱ ሁሉ ምስክር ይሆኑ ዘንድ እግዚአብሔር ፈቅዷል፡፡ «የነነዌ ሰዎች በፍርድ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፣ እነሆም «ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ» እንዲል /ሉቃ.11-32/፡፡ የነቢዩ የዮናስ ታሪክም እንደዚሁ ነው፡፡ የንስሐ ሰባኪ የሆነው ራሱም ከብዙ የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኋላ በንስሐ የተመለሰው ዮናስ የክርስቶስ ምልክት እንዲሆን እግዚአብሔር መፍቀዱ እግዚአብሔር ለተነሳሕያን የሚሰውን ክብር ያሳያል፡፡ ምንም እንኳን በዚህ ምድር ያለን ሰዎች የተነሣሕያንን ክብር ባናውቅም በሰማይ ያሉ መላእክት ግን በአንድ ኃጢአተኛ ንስሐ መግባት ታላቅ ደስታ ማድረጋቸው የንስሐን ክብር ያሳያል፡፡ ለዚህ ነው ለንስሐ የተዘጋጀ ልብን በማየት እግዚአብሔር አስቀድሞ ነነዌን «ታላቂቷ ከተማ» ብሎ የጠራት /ዮናስ.1-2/፡፡ ተነሣሕያን የእግዚአብሔር ይቅርታና ፍቅር የሚገለጥባቸው ሰዎች ናቸውና በእግዚአብሔርና በቅዱሳኑ ዘንድ የከበሩ ሰዎች ናቸው፡፡7. የእግዚአብሔርን ኃይል ማየት
በነነዌ ሰዎች የእግዚአብሔር ኃያልነት በግልጥ ተገልጧል፡፡ የእግዚአብሔር ኃያልነትም በትዕግሥቱ፣ በፍቅሩ፣ ፍጥረትን በመግዛቱ፣ ለሰው ልጆች በሰጠው ድንቅ ነፃነት ወዘተ ተገልጧል፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ አንዲትም ነፍስ ሳትጠፋ ሁሉም ይድኑ ዘንድ እግዚአብሔር ያሳየው የትዕግሥቱ ኃያልነት እንዴት ድንቅ ነው! የእግዚአብሔርን ፈቃድ ያስተምር ዘንድ ነቢይ የሆነው ዮናስ እንኳ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ትቶ ሲኮበልል በሔደበት ሁሉ እየተከተለ በተለያየ መንገድ ወደ መንገዱ እንዲመለስ ይሠራ ነበር፡፡ ምናልባትም ሰው ዮናስን ይህን ያህል አይታገሰውም፡፡ ሰዎችእግዚአብሔርን 'የመምከር' ዕድል ቢሰጠን «ጌታ ሆይ አንተ ሁሉን ማድረግ ትችላለህ፤ ከነዚህ ድንጋዮት እንኳ ለአብርሃም ልጆች ማስነሣት ትችላለህ፡፡ ለምን ዮናስን ትለምነዋለህ? ተወው ሌላ ነቢይ ወደ ነነዌ ላክ፡፡ ዮናስን ርግፍ አድርገህ ተወው ከነነዌ ሰዎች የራሱን ክብር አስቀድሟልና፡፡» እንል ይሆናል፡፡ በባሕሪዩ ታጋሽ የሆነው እግዚአብሔር ግን ዮናስ በንስሐ ይመለስ ዘንድ ጠብቆታል፤ በመጨረሻም ለክርስቶስ ምሳሌ የሚሆን ታላቅ ነቢይ አድርጎታል፡፡የነነዌ ጾም ከሰባቱ የቤተክርስቲያን አጽዋማት አንዱና የዐቢይ ጾም ማዘጋጃ ደወል ነው፡፡ ይህ የነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ በቤተክርስቲያናችን በጣም ታላቅ ዋጋ ያለውና የራሱ መዝሙር የሚዘመርለት፣ ቅዳሴ የሚቀደስበት ታላቅ መታሰቢያ ያለው ታሪክ ነው፡፡ ራሱ ጌታችንም የነዌ ሰዎችን የንስሐ ታሪክ በመጥቀስ አይሁድን ገስጾበታል፤ በፍርድ ቀንም በዚያ ትውልድ ዘንድ እንደሚፈርዱበት ተናግሯል፡፡ ይህም የሆነበት የነነዌ ሰዎች ደስ የሚያሰኝ የንስሐ ታሪክ ስላላቸው ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ይህን አስደሳች የንስሐ ታሪክ በጾመ ነነዌ ከሚነበቡ የቅዳሴ ምንባባት አንጻር ለመመርመር እንሞከራለን፡፡
ኃጢአት ከእግዚአብሔር መለየት እንደሆን ሁሉ ንስሐ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው፡፡ በዚህ ከእግዚአብሔር ሊለዩ የሚችሉ ብዙ ፈተናዎች ባለቡት ዓለም እስካለን ድረስ ሕይወታችን ሁሉ የንስሐ ጊዜ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ከሁሉም ጊዜ በተለየ ወደ እግዚአብሔር የምንመለስባቸው የጾም ወቅቶች ሲሆኑ ከእነዚህም ታላቁና ዋነኛው ዐቢይ ጾም ነው፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በዐቢይ ጾም ከእያንዳንዱ ምእመን ልቦና የንስሐ ፍሬን ትፈልጋለች፤ ያለትንሣኤ ልቦና /ንስሐ/ የክርስቶስን ትንሣኤ በእውነትና በደስታ ማክበር አይቻልምና፡፡ ለመሆኑ ከንስሐ የሚያሰናክሉን ነገሮች ምን ምን ናቸው? የነነዌ ሰዎች ታሪክ ስለዚህ ምን ያስተምረናል?
1. ቅንጦትን መውደድ
ምንም እንኳን በደፈናው ገንዘብ የኃጢአት ምንጭ ነው ባንልም እንደ ወንጌል ትእዛዝ በክርስቲያናዊ መንገድ ካልተያዘ ግን እግዚአብሔርን ሊያስረሳና የኃጢአት ማስፈጸሚያና ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ ብዙ ጊዜም ገንዘብና ባለጸግነት ከእግዚአብሔር በመለየታችን ያጣነውን ሰላምና ደስታ ለማግኘት ተስፋ የምንጥልበት ጣኦት ሆኖ ሊቀየር ይችላል፡፡ በሀብታችን በምናገኘው ጊዜያዊ ደስታና ሰላም ዘላለማዊውንና ፍጹምን የእግዚአብሔር ስጦታ መፈለግ፣ ወደ እግዚአብሔር መመለስን መናፈቅ ልናቆም እንችላለን፡፡ በዚህ መልኩ ብልጽግና ከንስሐ የሚያሰናክል ወጥመድ ይሆናል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሀብት እንኳ ቢሰጠን ለተቸገረ በመመጽወት፣ ልጆቻችን በክርስቲያናዊ መንገድ በማሳደግ፣ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በማፋጠን የእውነተኛ ደስታና የጽድቅ መንገድ እንድናደርገው እንጂ እግዚአብሔርን የተጠማች ነፍሳችንን ጥሪዋን በማደናቀፍና ጩኸቷን በማፈን በሥጋ ድሎት ውስጥ የምንደበቅበት መሣሪያ እንድናደረገው አይደለም፡፡ ለ«ታላቂቷ ከተማ» ነነዌም የጥፋት መንገድ የሆናት በብልጽገናዋና በታላቅነቷ እግዚአብሔርን ረስታ የኃጢአት ከተማ መሆኗ ነው፡፡ በነቢዩ በዮናስ ታሪክ ውስጥ ገንዘብ ለዮናስ ከእግዚአብሔር የመከለያ መሣሪያ ሲሆን እናገኘዋልን፡፡ «. .. ከእግዚአብሔርም ፊት ኮብልሎ ከእነርሱ ጋር ወደ ተርሴስ ይሔድ ዘንድ ዋጋ ሰጥቶ ወደ እርሷ /ወደ መርከቧ/ ገባ» እንዲል /ዮና፤1-3/፡፡
በዚህ ሰዓት ለዮናስ ገንዘብ ባይኖረው ይሻል ነበር፡፡ እኛም ቢሆን ከንስሐ የሚመልስ፣ ለኃጢአት መሣሪያ የሚሆን ሀብት ከሚኖረን በድኅነት ብንኖር ይሻለናል፡፡ ምንም እንኳ በቤተክርስቲያናችን ትውፊት ዐቢይ ጾም አብዝተን የምንጸልይበት፣ በጾም በስግደትና በምጽዋት ልናሳልፈው የሚገባ ወቅት ቢሆንም ፤ አሁን አሁን ግን ገንዘብ ማግበስበሻ እየሆነ እንደሆነ እናያለን፡፡ በመሠረቱ በጾም ወቅት ከሆዳችን የምንቀንሰው ገንዘብ እንድናጠራቅመው ሳይሆን እንድንመጸወተው የሚገባ ነው፡፡ ለማጠራቀምማ የማያምኑ ሰዎችስ ምግብ ይቀንሱ የለ? ለዚህ ነው በነነዌ ጾም በመጀመሪያው ቀን /ሰኞ/ የሚነበበው የቅዱስ ያዕቆብ መልእክት «አሁንም እናንተ ባለ ጠጎች ስለሚደርስባችሁ ጭንቅ ዋይ ዋይ እያላችሁ አልቅሱ፡፡ ሀብታችሁ ተበላሽቷል፣ ልብሳችሁም በብል ተበልቷ፡፡ ወርቃችሁም ብራችሁም ዝጓል፤ ዝገቱም ምስክር ይሆንባችኋል፤ ሥጋችሁንም እንደ እሳት ይበላል፡፡ ለኋለኛው ቀን መዝገብን አከማችታችኋል፡፡ እነሆ እርሻሁን ያጨዱት የሠራተኞች ደመወዝ በእናንተ ተቀምቶ ይጮኻል፣የአጫጆችም ድምፅ ወደ ጌታ ጸባዖት ጆሮ ገብቷል፡፡ በምድር ላይ ተቀማጥላችኋል፤ በሴሰኝነትም ኖራችኋል፤ ለእርድ ቀን እንደሚወፍር ልባችሁን አወፍራችኋል፡፡» በማለት አስፈሪ ተግሳጽ የሚያስተላልፈው፡፡ ስለዚህ በዐቢይ ጾም አብዝተን የምንመጸውትበት፣ ከእግዚአብሔር የሆነውን ስጦታ የምንፈልግበት፣ የንስሐ ጊዜ ሊሆን ይገባል፡፡2. ለኃጢአት ሌላ ተጠያቂ መፈለግ
ሌላው ከንስሐ ሲያርቀን የሚገኘው ምክንያት በሰዎች መፍረድ ነው፡፡ በሰዎች የሚፈርድ ሰው ራሱን የሚያጸድቅ ነው፡፡ ራሱን ያጸደቀ ደግሞ ንስሐ መግባትና ከኃጢአት መመለስ ዳገት ይሆንበታል፡፡ ከነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ ውስጥ ለንስሐ በጣም አስቸጋሪ የነበረው ነቢዩ ዮናስ ነው፡፡ መርከበኞቹና የነነዌ ሰዎች በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ወደ እግዚአብሔር ሲመለሱ ዮናስ ግን ከታሪኩ መጀመሪያ እስከ መጨረሻዋ ጊዜ ድረስ በእግዚአብሔር ያጉረመርም ነበር፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ከእግዚአብሔር መኮብለሉና የነነዌ ሰዎችን ድኅነት መቃወሙን እንደ ስህተት እንጂ እንደራሱ ስህተት አለመቁ ጠሩ ነው፡፡ ለዚህ ነበር ከእግዚአብሔር ኮብልሎ ሲሔድ እንኳ ምንም ዓይነት ጭንቀት ሳይሰማው «በከባድ እንቅልፍ» ተኝቶ የነበረው /ዮና.1-5/፡፡ በተመሳሳይ መልኩ አንዳንድ ሰዎች ለራሳቸው ኃጢአት እግዚአብሔርን ተጠያቂ ሲያደርጉ ሌሎች ደግሞ ሰዎችን ተጠያቂ ያደርጋሉ፡፡ በዚህም በራሳቸው ከመፍረድ ይልቅ በሰዎች መፍረድ ይጀምራሉ፤ ወይም የኃጢአታቸው ምክንያት እግዚአብሔርን አድርገው ይገኛሉ፡፡ ነቢዩ ዮናስ የራሱን ክብር ፈላጊነት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ምሕረት የኃጢአቱ ምክንያት ማድረጉ የሚያስገርም ነው፡፡ ይህም ለብዙ ጊዜ ከንስሐ እንዳዘገየው ከታሪኩ እንማራለን፡፡ በተቃራኒው ለንስሐ ቅርብ የሆኑት መርከበኞች በዮናስ ላይ ለመፍረድ ምን ያህል እንደተጨነቁ ስናይ ቀድሞውኑ በዮናስ አለመታዘዝ ምክንያም ቢሆን እግዚአብሔር ወደ ንስሐ ሊመልሳቸው የፈለገ ይህን አይቶ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡3. የእግዚአብሔርን ተግሳጽ አለመቀበል
በነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ሰዎችን ሲገስጽ እንመለከታለን፡፡ ነቢዩ ዮናስን በማዕበል፣ ወደባሕር እንዲወረወር በማድረግ፣ አሳ አንበሪ እንዲውጠው በማድረግእግዚአብሔር ወደ ትክክለኛ መንገዱ ሊመልሰው ቢጥርም በዚህ ሁሉ ሊመለስ አልቻለም፤ ከአሳ አንበሪ አፍ ወጥቶ ሔዶ ቢሰብክም እግዚአብሔር ይቅር ሲላቸው ግን በእግዚአብሔር ላይ ማጉረምረም ጀምሯልና፡፡ ድሮም ቢሆን በፍርሃት እንጂ ስህተቱን ተቀብሎ አልነበረም ወደ ነነዌ ሔዶ የሰበከው፡፡ ግዕዛን የሌላቸው ፍጥረታት /ነፋስ፣ አሳ አንበሪ፣ ትል፣ ፀሐይ/ እንዴት እንደሚታዘዙለት እርሱ ግን ታላቅ ነቢይ ሲሆን አልታዘዝም ማለቱን በማሳየትም ገስጾታል፡፡ በመጨረሻም ለንስሐ በቅቷል፡፡ መርከበኞቹም በመርከባቸው ላይ የተነሣው ማዕበል ተግሳጽ ሆኗቸው ወደ ንስሐ ተልሰዋል፡፡ ከዘላለም ሕይወት እንዳንለይ አጥብቆ የሚፈልገው እግዚአብሔር ልዩ ልዩ መከራዎችንም በማምጣት ወደ ንስሐ እንድንመለስ ያደርጋል፡፡ ለዚህ ተግሳጽ ግን በትክክለኛ ወይም በተሳሳተ መንገድ መልስ ልንሰጥ እንችላለን፡፡ ካወቅንባቸውና ከተጠቀምንባቸው ችግሮችና መከራዎች ወደንስሐ የሚመሩ መንገዶች ናቸው፡፡ የነነዌ ታሪክም የሚነግረን ይህንኑ ነው፡፡ በነነዌ ጾም በቅዳሴ የሚነበቡት የሚከተሉት ምንባባትም በአጽንኦት የሚገልጹት ይህንኑ ነው፡፡ምስባክ:- «ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በላዬ አለፈ፡፡
እግዚአብሔር በቀን ቸርነቱን ያዛል በሌሊትም ዝማሬው በእኔ ዘንድ ይሆናል
የእኔ ስዕለት ለሕይወቴ አምላክ ነው፡፡» /መዝ.41-7-8/መልእክት:- «. . . ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል. . .» /ሐዋ.14-22/፡፡
በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ አሳዛኙ ነገር ሰው ካለፈ ሕይወቱ አለመማሩ ነው፡፡ በነቢዩ በዮናስ ታሪክም የምናገኘው ይህንኑ ነው፡፡ እግዚአብሔር የተሳፈረበትን መርከብ ካናወጠ፣ ዮናስ በአሳ አንበሪ እንዲዋጥ ካደረገ በኋላ እንኳ እግዚአብሔር በነነዌ ሰዎች ላይ ያሳየው ምሕረት ዮናስ ሞትን እስኪመኝ ድረስ እንዲያዝንና በእግዚአብሔር ላይ እንዲያጉረመርም አድርጎታልና፡፡ በእኛም ሕይወት ተመሳሳይ ተግሳጻት ከእግዚአብሔር ዘንድ ቢመጣም ከኃጢአት ባለመመለስ ከዮናስ ያልተለየ መልስ ነው የምንሰጠው፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ራሳችንን የምናይበት፣ በሕይወታችን ያደረጋቸውን የእግዚአብሔር ሥራዎች የምንመረምርበት፣ በውስጣችን ያደፈጡትን አውሬዎች የምናድንበት የተረጋጋና ሰፋ ያለ ጊዜ ስለሌለን ነው፡፡ ይህን አጥብቃ የተረዳችው ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በልዩ ልዩ መንገድ የሚጠራንን የእግዚአብሔር ድምፅ የምናዳምጥበት፣ በመልካም ምክንያቶች የተሸፈኑ ነገር ግን መልካም ያልሆኑና መልካም ልንሠራበት የምንችለውን የሕይወት ጊዜዎችን የሚያቃጥሉ ከንቱ ምኞቶቻችን፣ የማይጨበጡና የማይደረስባቸው «ክፉ ተስፋዎቻችን» ሁሉ የምንመረምርበት፣ መልካሟንና እውነተኛዋን ነገር ግን አስቸጋሪዋንና ጠባቧን የሕይወት መንገዳችን አጉልተን «የምናስምርበት» ሰፋ ያለ ጊዜ ሰጥታናለች፤ ይህም ዐቢይ ጾም ነው፡፡ በዚህ ጊዜ በአግባቡ ከተጠቀምንበትም የዚህን አስቸጋሪና አወናባጅ ዓለም በድል የተወጡ ሰዎች የሚያዩትን የዘለዓለማዊን ሕይወት «ቀብድ» የትንሣኤውን ብርሃን እናያለን፡፡ ዐቢይ ጾምን እንደሚገባ ያላሳለፈ ክርስቲያን ግን የትንሣኤን ድግስ በልቶ ሆዱን ይሞላ እንደሆነ እንጂ የትንሣኤን ታላቅ ደስታ መቅመስ አይችልም፡፡ ስለዚህም ዐቢይ ጾም ለክርስቲያን ታላቅ ስጦታ መሆኑን ልናውቅ ይገባል፡፡ ለዚህም ነው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ስለጾም በጻፉት መጽሐፋቸው «በዐቢይ ጾም ሕይወቱን ያልቀየረ ክርስቲያን በሌሎች አጽዋማት ይቀይራል ማለት ይከብዳል» በማለት የጻፉት፡፡4. ክፉ እኔነት
በዮናስ ታሪክ ውስጥ ከብዙ የዮናስ ስህተቶች ጀርባ የነበረውና ንስሐውን ያዘገየበት ታላቁ መሰናከል ክፉ እኔነት ነው፡፡ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ የነነዌ ሰዎችን ድኀነት ሳይሆን የራሱን ክብር እንዲመለከት ያደረገው በዮናስ ሕይወት ውስጥ በጥልቅ የተተከለ ክፉ እኔነቱ ነው፡፡ በዚያ ሁሉ ታሪክ ውስጥ በርግጥም ዮናስ ስለራሱ እንጂ ስለሰዎች ሲያስብ አልታየም፡፡ ነቢዩ ዮናስ «እኔ ሐሰተኛ ነቢይ ከምባል የነነዌ ሰዎች መጥፋት ይሻላል»«የዮናስ አምላክ ቃሉን ይቀይራል ከምባል የነነዌ ሰዎች ይጥፉ» ብሎ ያስብ እንጂ እግዚአብሔር ግን አላለም፡፡ አመድና ትቢያ የሆነው የሰው ልጅ ስለክብሩ ሲጨነቅ ክብር የባሕሪዩ የሆነ ሩህሩህ አምላክ ግን ማንም እንዲጠፋ አልፈቀደም፡፡ይህን ሁሉ የሕይወታችን ውጥንቅጥ እንመረምርበት ዘንድ ታላቁ የቤተክርስቲያን ስጦታ ዐቢይ ጾም እነሆ፡፡
የእውነተኛ ንስሐ ውጤቶች በነነዌ ሰዎች ታሪክ
5. የዘላለም ሕይወት ተስፋ
ነነዌ የጥፋት ፍርድ ከተፈረደባት በኋላ የመኖር ተስፋ የተሰጣት ከተማ ናት፡፡ በሌላ አነጋገር ነነዌ ሞታ የተነሣች ከተማ ናት ማለት ይቻላል፡፡ ነቢዩ ዮናስም ወደ ባሕር ከተጣለ፣ በአሳ አንበሪ ሆድ ውስጥ ካደረ በኋላ የመኖር ተስፋ የተሰጠው ሰው ነው፡፡ መርከበኞችም መርከባቸው በማዕበል ከተመታች በኋላ፣ ማዕበሉ ካሸነፋቸው በኋላ በእግዚአብሔር ምሕረት ሌላ የመኖር ተስፋ የተሰጣቸው ሰዎች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የነነዌ ታሪክ የተስፋ ታሪክ ነው፡፡ንስሐም በኃጢአት ከሞቱ በኋላ እንደገና የመኖር ተስፋ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች የዘለዓለም ሕይወትን ተስፋ ማድረግ ይከብዳቸዋል፤ ለዚህም ምክንያቱ በንስሐ አለመኖራቸው ነው፡፡ ሰው ያላየውን ነገር እንዴት ይናፍቃል? የማያውቀውን ነገርስ እንዴት ተስፋ ያደርጋል? በንስሐ የሚኖር ሰው ግን የዘለዓለም ሕይወት ቀብድ የሆነ ትንሣኤ ልቦናን ይነሣልና የዘለዓለም ሕይወትን በተስፋ ይናፈቃሉ፡፡ ዐቢይ ጾምንም በንስሐና ራስን በመመርመር ያሳለፈ ሰው በትንሣኤው ትንሣኤን ይቀምሳልና ዘለዓለማዊውን ትንሣኤ በተሰፋ ይናፍቃል፡፡
በነነዌ ጾም የሚነበቡ የቅዳሴ ምንባባትም ይህን እንደሚከተለው ይገልጻሉ፡-
«. . . ትዕግሥትም ፈተናን፣ ፈተናም ተስፋን እንዲያደርግ እያወቅን በመከራችን ደግሞ እንመካለን፡፡ በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም፡፡» /ሮሜ.5-4-5/፡፡6. በእግዚአብሔር ዘንድ መከበር
በንስሐ የተመለሰችው ነነዌ በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ ከብራለች፡፡ የነነዌ ሰዎች ንስሐ በማይገቡ ዘንድ በትውልዱ ሁሉ ምስክር ይሆኑ ዘንድ እግዚአብሔር ፈቅዷል፡፡ «የነነዌ ሰዎች በፍርድ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፣ እነሆም «ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ» እንዲል /ሉቃ.11-32/፡፡ የነቢዩ የዮናስ ታሪክም እንደዚሁ ነው፡፡ የንስሐ ሰባኪ የሆነው ራሱም ከብዙ የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኋላ በንስሐ የተመለሰው ዮናስ የክርስቶስ ምልክት እንዲሆን እግዚአብሔር መፍቀዱ እግዚአብሔር ለተነሳሕያን የሚሰውን ክብር ያሳያል፡፡7. የእግዚአብሔርን ኃይል ማየት
በነነዌ ሰዎች የእግዚአብሔር ኃያልነት በግልጥ ተገልጧል፡፡ የእግዚአብሔር ኃያልነትም በትዕግሥቱ፣ በፍቅሩ፣ ፍጥረትን በመግዛቱ፣ ለሰው ልጆች በሰጠው ድንቅ ነፃነት ወዘተ ተገልጧል፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ አንዲትም ነፍስ ሳትጠፋ ሁሉም ይድኑ ዘንድ እግዚአብሔር ያሳየው የትዕግሥቱ ኃያልነት እንዴት ድንቅ ነው! የእግዚአብሔርን ፈቃድ ያስተምር ዘንድ ነቢይ የሆነው ዮናስ እንኳ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ትቶ ሲኮበልል በሔደበት ሁሉ እየተከተለ በተለያየ መንገድ ወደ መንገዱ እንዲመለስ ይሠራ ነበር፡፡ ምናልባትም ሰው ዮናስን ይህን ያህል አይታገሰውም፡፡ ሰዎችእግዚአብሔርን 'የመምከር' ዕድል ቢሰጠን «ጌታ ሆይ አንተ ሁሉን ማድረግ ትችላለህ፤ ከነዚህ ድንጋዮት እንኳ ለአብርሃም ልጆች ማስነሣት ትችላለህ፡፡ ለምን ዮናስን ትለምነዋለህ? ተወው ሌላ ነቢይ ወደ ነነዌ ላክ፡፡ ዮናስን ርግፍ አድርገህ ተወው ከነነዌ ሰዎች የራሱን ክብር አስቀድሟልና፡፡» እንል ይሆናል፡፡ በባሕሪዩ ታጋሽ የሆነው እግዚአብሔር ግን ዮናስ በንስሐ ይመለስ ዘንድ ጠብቆታል፤ በመጨረሻም ለክርስቶስ ምሳሌ የሚሆን ታላቅ ነቢይ አድርጎታል፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)